መልአከ መንግሥተ ሰማያት[]
- የመንግሥተ ሰማያትን መልእክት ለሰው ልጆች ከሚያመጣው ከመልአከ መንግሥተ ሰማያት ጋራ አራተኛው ቁርባን ነው።
- ከመላእክት ጋራ የሚሔድ ከደመናት በላይ ለመምጠቅ ይማራልና፣ የሕይወት ቅዱስ ዛፍ በሚቆምበት በዘላለማዊው ባሕር ውስጥ መኖሪያው ይሆናል።
- ሞት ታላቅ ምስጢሩን እስኪገልፅ ድረስ አትቆይ። እግርህ በመሬቱ አፈር ላይ እየተራመደ የሰማዩን አባትህን ካላወቅክ፣ በዘመነ መንግሥተ ሰማያት ከጥላ በቀር ምንም አይኖርህም።
- እዚህም አሁንም ምስጢሩ ይገለፃል፤ እዚህም አሁንም መጋረጃው ይነሣል። አትፍራ፣ አንተ ሰው ልጅ ሆይ።
- የመልአከ መንግሥተ ሰማያትን ክንፍ ያዝ፤ የመንገድም ፍጻሜ ለመድረስ ዘወትር ወደ ዞሩት ወደ ከዋክብት፣ ወደ ጨረቃ፣ ወደ ፀሐይ፣ ወደማይቋረጥ ብርሃን ጎዳና ብረር፤ ወደ ሰማዩ ዘላለማዊ ሕይወትም ባሕር ምጠቅ። [በያሽት 13:57-58]
ሥላህ።